Рет қаралды 26,155
ልቤ ሰላም ሲያጣ መከራው ሲበዛ
ወደማን አያለሁ ኢየሱስ ካንተ ሌላ
ልቤ ሰላም ሲያጣ ወጀቡ ሲበዛ
ወደማን አያለሁ የሱስ ካንተ ሌላ
ወየሁ ጠፋሁ ብዬ ሳለቅስ ሳነባ
ብቻዬን ነኝ ብዬ ስቆዝም ስከፋ
የዘላለም አምላክ ኢየሱስ ደረሰልኝ
የልቤን ተናግሮ በሰላም ሂድ አለኝ
አወድሃለሁ አወድሃለሁ አወድሃለሁ
ሚገባኝ ይሄ ነው (፪x)
አዝ፡-ዝና ዝናዬ ዝና ዝናዬ
አንተው ነህና (፪x)
ባገልግሎቴ ላይ ዝናዬ
ክብር ያሳየኅኝ ዝናዬ
የማዕረግ ልብሴ ዝናዬ
የክብር ሽልማት ዝናዬ
ብኖር ላትጠቀም ሞቼ ላትጎዳ
በደምህ ከፈልከው የሕይወቴን ዕዳ
በደለኛው ልቤን በደምህ ቀድሰህ
ሕይወትን ሸለምከኝ ደህንነት አልብሰህ
ጉድጓዴን ስቆፍር ድንበሬን ልገፋ
ምሕረትህ ገደበኝ ታዝቦ ስገፋ
ነፍሴም ተመለሰች ከርስቷ ግዛት
በመስቀሉ ስራህ በጻድቁ ሞት
አወድሃለሁ አወድሃለሁ አወድሃለሁ
ሚገባኝ ይሄ ነው (፪x)
አዝ፡- ዝና ዝናዬ ዝና ዝናዬ
አንተው ነህና (፪x)
ባገልግሎቴ ላይ ዝናዬ
ክብር ያሳየኅኝ ዝናዬ
የማዕረግ ልብሴ ዝናዬ
የክብር ሽልማት ዝናዬ
የሰጠኝን ላጣ የእጁን ተመኝቼ
ምሕረትን ስጠማ ፍሬዋን በልቼ
የጽድቅን ጥያቄ በልጁ መልሶ
ፈቃዱን አጸና መርገሜን ፈውሶ
አዝ፡- ዝና ዝናዬ ዝና ዝናዬ
አንተው ነህና (፪x)
ባገልግሎቴ ላይ ዝናዬ
ክብር ያሳየኅኝ ዝናዬ
የማዕረግ ልብሴ ዝናዬ
የክብር ሽልማት ዝናዬ