Рет қаралды 92
ወደ ሀገር ቤት ለምትጓዙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት
አንድ ሚሊየን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት ወደ ሀገር ቤት እንዲመጡ በቀረበው ሀገራዊ ጥሪ መሰረት የዳያስፖራ አባላት ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ የዳያስፖራውን የቆይታ ጊዜ የተቀናጀ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ ለዳያስፖራው ሁለገብ መረጃ የሚያቀርብና የዳያስፖራ አባላትን መረጃዎች ለማሰባሰብና ለማደራጀት የሚያስችል ወጥ የሆነ የኦንላይን የመረጃ ድረ-ገጽ ያዘጋጀ ሲሆን የድረ-ገጹ አድራሻም www.greatethiopianhomecoming.org ነው፡፡ የዳያስፖራ አባላት በድረ-ገጹ register በሚለው ታብ በመግባት በሚያገኙት ፎርም እንዲመዘገቡ እየጠየቅን፣ ከድረ-ገጹ መረጃዎችን ማየትና ያሏቸውን ጥያቄዎች በመጻፍ ቀጥተኛ ምላሽ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ