Рет қаралды 5,558
#ትዕግስት
‹‹እነዚያ በመታገሳቸው የገነትን ሰገነቶች ይምመነዳሉ፡፡ በእርሷም ውስጥ ውዳሴንና ሰላምታን ይስሰጣሉ፡፡›› አል ፉርቃን:75)
አቡል ዐባስ እንዲህ ብሏል "ትዕግስት ማለት ነፍስን ከምትጠላው ነገር ማገድ፤ አንደበትን ስሞታ ከማሰማት ማቀብ፤ ሐዘንን ችሎ መሸከም ነው፤ (ከመቸገር በኋላም) መጨረሻው ነፃ መውጣትን መጠበቅ ነው፡፡"
ምድር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ናት። በአንዱ ገጽታዋ ደስታን፣ እረፍትን፣ ፌሽታን፣ ድሎትን፣ መተሳሰብን፣ ፍቅርን... ይዛለች። በሁለተኛው ገጽታዋ ደግሞ ሀዘንን፣ ርሃብን፣ ጭንቀትን፣ ፈተናን፣ ውጥረትን የመሳሰሉትን አቅፋለች።
አቢ የህያ ሱሀይብ ኢብን ሲናን(ረ.ዐ) እንደተናገረው፦
የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-
‹‹የሙዕሚን ጉዳይ ያስገርማል! ጉዳዩ በጠቅላላ ለእርሱ ኸይር ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለሙዕሚን እንጂ ለማንም አይሆንም፡፡ መልካም ነገር ሲገጥመው ያመሰግናል በዚህም መልካም ይሆንለታል፡፡ መጥፎ (ችግር) ሲገጥመው ይታገሳል ለርሱም ኸይር ይሆንለታል፡፡›› (ሙስሊም)
አዎ ሰው በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው ብዙ ጉዳይ ይገጥመዋል፤ ያጋጠመውን ጉዳይ ታግሶ ማለፍ ግድ ይለዋል። ጣፋጩን ለማግኘት መራራውን ማለፍ ይጠበቅበታልና።
‹‹ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎች በመቀነስ በእርግጥ እንፈትናችኃለን፡፡ ታጋሾችንም (በጀነት) አበስራቸው›› (አል በቀራህ:155)
‹‹ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መኾኑን ሊሞክራችሁ ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው፡፡ እርሱም አሸናፊው መሓሪው ነው፡፡››(አል ሙልክ:2)
‹‹አላህ እንዲህ ብሏል ባሪያዬን ሁለት ተወዳጆቹን (ዓይኖቹን) በመውሰድ ፈትኜው በዚያም ከታገሰ በምትካቸው ጀነትን እሰጠዋለሁ›› (ቡኻሪ)
አላህ(ሱ.ወ) ባሪያውን እንደሚፈትን እና ፈተናውን ካለፈ ደምወዙ ከፍ ያለ እንደሆነ በግልጽ አስቀምጦልናል።
ምንዳው ያለ ገደብ ነው እየተባልን መታገስ እንዴት ያቅተን?
«ታጋሾች ምንዳቸው ሚከፈላቸው ያለ ግምት ነው።» (አል ዙሙር 10)
የብዙዎች የተሳሳተ እሳቤ ትዕግስት የሚደረግበትን ጊዜ በቅጡ አለማወቅ ነው። ትዕግስት ማድረግ የሚያስፈልገው የገጠመህ ጉዳይ ካለፈ ወይም ከተረጋጋ በኋላ ሳይሆን ያልጠበቅከው ነገር ባጋጠመህ ወቅት ነው። እርግጥ ጉዳዩ ካለፈ በኋላም ትዕግስት ያስፈልጋል።
‹‹ሰብር በሀዘን የመጀመሪያ ክፍል ነው›› (ቡኻሪ ሙስሊም)
እንቅስቃሴዎችህ በሙሉ በሶብር የታገዙ መሆን አለበት። የምትፈልገውን ለማግኘት መታገስና መጽናት ይጠበቅብሃል።
‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ ታገሱ›› (አል-ዒምራን፡200)
#ሶብር_ሶስት_ክፍሎች_አሉት፡-
1. የአላህ ትዕዛዝን በመፈፀም ላይ ትዕግስት ማድረግ፡፡
2. አላህ ክልክል ባደረጋቸው ነገሮች ላይ (በመራቅ) መታገስ፡፡
3. በአላህ ውሳኔ ላይ ሶብር ማድረግ፡፡ (መጥፎ የተባሉ ነገሮች በሚያጋጥሙን ጊዜ የአላህ ውሳኔ መሆኑን አውቆ በፀጋ መቀበል)
‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በመታገስና በሶላት ተረዳዱ፡፡ አላህ ከታጋሾች ጋር ነውና›› (አል በቀራህ፡153)
‹‹ከእናንተም ታጋዮቹንና ታጋሾቹን እስከምናውቅ፣ ወሬዎቻችሁንም እስከምንገልፅ ድረስ በእርግጥ እንሞክራችኃለን›› (ሙሀመድ፡31)
«...እነሆ! የሚጠነቀቅና የሚታገስ ሰው (አላህ ይክሰዋል)፡፡ አላህ የበጎ አድራጊዎችን ዋጋ አያጠፋምና» አለ፡፡›› (ዩሱፍ፡90)
‹‹ከመልዕክተኞች የቆራጥነት ባለቤቶች የኾኑት እንደ ታገሱ ሁሉ ታገስ፡፡›› (አል-አህቃፍ፡35)
‹‹በጊዜያቱ እምላለሁ፡፡ ሰው ሁሉ በእርግጥ በኪሳራ ውስጥ ነው፡፡ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡›› (አል-ዐስር፡1-3)
በዚህች ምድር ያለ ትዕግስት ምንም የሚሆን ነገር የለም፤ ለዚህም ነው አላህ አጽንዖት ሰጥቶ ምንዳው የማይገመት ያደረገው።
«ታጋሾችን አበስራቸው›› (አል በቀራህ:155)
.