Рет қаралды 12,582
ከሐምሌ 30 እስከ ነሐሴ 02/2013 ድረስ በሐዋሳ እናት አጥቢያ በተዘጋጀው ዓመታዊ የአባቶች ጉባዔ ላይ "ንጉሡንና ጽዮንን እያየህ ኑር እያየህ ሙት" በሚል ርዕስ በወንጌላዊ ደረጀ ከበደ የቀረበ መደመጥ ያለበት መልዕክት
ኢሳ 33:17:-... ጽዮንን ተመልከት...ዓይኖችህ ኢየሩሳሌምን ያያሉ።
ዕብ 11:13:-... የሚበልጠውን እርሱም ሰማያዊ አገር ይናፍቃሉ...
#ንጉሱንና_ጽዮንን(ኢየሩሳሌምን)_እያየህ_ኑር_እያየህ_ሙት።
- ገሃነምን የምናሸንፍበት ብቸኛው መንገድ ንጉሡንና ጽዮንን ማየት ነው።
ራዕ 21:1:-...አዲሲቱ ኢየሩሳሌም ለባልዋ እንደተሸለመች ሙሽራ ተዘጋጅታ ከሠማይ ስትወርድ አየሁ።...
ራዕ 17:1
- የጋለሞታዋ መንፈስ ዓለምን ተቆጣጥሮ ነው ያለው። የምድር ርኩሰት እናት ነች።
- ሁለት የሚታዩ ነገሮች አሉ 👇👇
👉1. አንድ የሚገለጥ ንጉሥና አገር አለ
👉2. እዚሁ እያጓጓች ልታስቀር የምትጥር የምድር ርኩሰት ንግሥት አለች
- አባቶቻችን ሲገረፉም፣ ሲደበደቡም፣ በመጋዝ ሲሰነጠቁም ዓይናቸው ያይ የነበረው ንጉሡንና አገራቸውን ነበር።
- ጽዮንን አሁን የሚያያት ነው የሚወርሳት።
- እግዚአብሔር አምላካችን ተብሎ ሊጠራ የማያፍርብን የምድርን ርኩሰት ንቀን ዓይናችንን ወደ እርሱ ስናነሳ ብቻ ነው።
- የምድር ርኩሰት ንግሥት የሰውን ልጅ በምቾት፣ ጊዜ በማሳጣት፣ አንዳንዴም በጥልቅ ድህነት ንጉሡን እንዳናይና እንድንረሳው ታደርጋለች።
** ንጉሡንና ጽዮንን እያየህ ኑር እያየህ ሙት **
- ኢዮብ ሚስቱንም ሰይጣንንም ያሸነፈበት ሚስጥር ንጉሡን ብቻ ያይ ስለነበር ነው።
(ኢዮብ 19:25
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ እኔን ግን የሚቤዠኝ ሕያው እንደ ሆነ፥ በመጨረሻም ዘመን በምድር ላይ እንዲቆም፥
²⁶ ይህ ቁርበቴም ከጠፋ በኋላ፥ በዚያን ጊዜ ከሥጋዬ ተለይቼ እግዚአብሔርን እንዳይ አውቃለሁ።
²⁷ እኔ ራሴ አየዋለሁ፥ ዓይኖቼም ይመለከቱታል፥ ከእኔም ሌላ አይደለም። ልቤ በመናፈቅ ዝሎአል።)
- ኢዮብ በተስፋ የሚቤዠኝን አየዋለሁ አለ፤ እኛ ግን የተቤዠንን እናየዋለን።
- የምድር እናት ምድርን በሶስት ነገር ተቆጣጥራዋለች👇👇👇
👉1. በርኩሰት:- የወንድ ለወንድ እና የሴት ለሴት ጋብቻን በምድር በማሰራጨት።
- የጋለሞታን መንፈስ (አንድ ባል የሌላት) በምድር ላይ በመልቀቅ አማልክቶችን አብዝታለች።
- ከእግዚአብሔር ይልቅ በእኛ ላይ የሚሰለጥን ዕውቀት፣ ሀብት፣ ሰው፣ ክፉ ቴክኖሎጂ ሌላም ነገር በሙሉ አማልክት ነው።
👉2. በስካር:- የሰዉን ሕይወት በሙሉ በሚያጓጓ እና በሚያሰክር (ገንዘብን በመውደድ፣ በኑሮ ውድነት፣ በበሽታ...) ነገር ታመሰቃቅላለች።
- ሰካራም ጉዱን የሚያውቀው ሲነጋበት ነው።
ራእይ 18:1:-...
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² በብርቱም ድምፅ፦ ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤
… ...
⁴ ከሰማይም ሌላ ድምፅ ሰማሁ እንዲህ ሲል፦ ሕዝቤ ሆይ፥ በኃጢአትዋ እንዳትተባበሩ ከመቅሠፍትዋም እንዳትቀበሉ ከእርስዋ ዘንድ ውጡ፤
⁵ ኃጢአትዋ እስከ ሰማይ ድረስ ደርሶአልና፥ እግዚአብሔርም ዓመፃዋን አሰበ።
- ጽዮንን አለማየትና አለመጠበቅ ሲነጋ ዋይታ ነው።
- እግዚአብሔር ከወደደኝ እርሱንና መንግሥቱን ያሳየኝ።
- ሰይጣን የሚያሳየን ብዙ ነው አጥርተን/ለይተን ማየት የእኛ ድርሻ ነው።
- አሁን የምንኖረው ሕይወት ነው መጨረሻችንን የሚያሳውቀን። አሁን የምናየውን ነው ኋላ የምናገኘው።
ራእይ 22:12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።
…
¹⁷ መንፈሱና ሙሽራይቱም፦ ና ይላሉ። የሚሰማም፦ ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።
- የእኛ መንፈስ ና ይላል ወይስ???
- ሰማይን የሚያይ ሰማይ ይሄዳል ምድርን የሚያይ ምድር ይቀራል።
*****
ዓይኖቼን ከሚታየው ነገር አንስቼ
በሰጠኸኝ ተስፋ በእምነቴ በርትቼ
ደመናና ንፋሱን መጠበቄን ትቼ
ግራ ቀኜን ሳልል ወደአንተ አቅንቼ
አንተን ብቻ እያየሁ በትዕግስት ኖራለሁ
አንተን ብቻ እያየሁ እጠብቅሃለሁ
አንተን ብቻ እያየሁ ተስፋ አደርግሃለሁ
አንተን ብቻ እያየሁ በእምነት ኖራለሁ
ቢጎድል ባይጎድል እኔ አላማርርም
ዘገየብኝ ብዬ አላጉረመርምም
ነገሬን በጊዜው ውብ ታደርገዋለህ
በትዕግሥት ልጠብቅ አምላኬ ታማኝ ነህ
ለእኔ ታማኝ ነህ አንተ |3x
ለእኔ መልካም ነህ አንተ |3x
ለእኔ በቂ ነህ አንተ |3x
*****