ዓላማው:
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሁሉ ያዘጋጀውን የምህረቱንና የማዳኑን የምስራች የክርስቶስን ወንጌል ገና ላልሰሙና ላላመኑበት እንዲደርስና ወንጌሉን ሰምተው የተቀበሉት መንፈሳዊ ህይወት እንድታነጽ መልዕክቶችን በዝማሬ: በስብከት/ትምህርት: በግጥምና በተለያዩ ዘይቤዎች ያለ ዋጋ በነፃ ማስተላለፍ ነው::
- ሉቃ. 24 [47 በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል፡ ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል።]
- ሮሜ 10:13-17 [13 የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና። 14፤ እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ? ... 17 እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።]
- 1ኛ ጴጥ. 2:2-5 [2-3 ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። ..... በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።]
- 1ኛ ቆሮ. 12:4-7 [4 የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤ 5 አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው ጌታም አንድ ነው፤ 6 አሠራርም ልዩ ልዩ ነው፥ ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው። 7 ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን መግለጥ ለእያንዳንዱ ለጥቅም ይሰጠዋል።]
- ማቴ. 10:7-8 [7 ሄዳችሁም፦ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች፡ ብላችሁ ስበኩ። 8 ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ።]
Claim copy right? Contact
[email protected]