Рет қаралды 4,729
#fana_tv #fana_digital #fana_tech
በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት እያገለገለ ይገኛል፡፡ ቻላቸው ተማሪ ሳለ የሚሰራው ፕሮጀክት ችግር ፈቺ እንዲሆን ይፈልግ ነበር፡፡ ይህንንም መሰረት በማድረግ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ወደ ሚገኘው ‘’ትራዲሽናል ላብራቶሪ’’ ውስጥ በአድቫይዘሩ ወይንም በአማካሪው አማካኝነት ይገባል፡፡ በዚያም በአድካሚ ሁኔታ ክር የሚያጠነጥኑ አንድ ሸማኔ ያገኛል፡፡ ይህ ሁኔታም የፈጠራ ስራው መነሻ ሆኖት በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠራ አውቶማቲክ መሸመኛ ማሽንና ማጠንጠኛ እንዲሰራ አብቅቶታል፡፡ ከፋና ዲጂታል ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል፡፡