Рет қаралды 282
አቡ ሁረይራ (ረድየሏሁ ዓንሁ) ባስተላለፉት ሐዲስ ነቢዩ (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) ...
አቡ ሁሬይራ (ረድየሏሁ ዓንሁ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብሏል 'ሙስሊም በሙስሊም ላይ ያሉት መብቶች 5 ናቸው፤ ሰላምታን መመለስ፣ በሽተኛን መጠየቅ፣ ጀናዛ መሸኘት፣ ጥሪን (ግብዣን) ማክበር፣ ላስነጠሰው በጎ ምኞትን መግለፅ፡፡'
በሌላ ዘገባ ደግሞ 'ሙስሊም በሙስሊም ላይ ያሉት መብቶች 6 ናቸው፤ ስታገኘው ሰላምታ አቅርብለት፣ ሲጋብዝህ ግብዣውን ተቀበል፣ ካንተ ምክር ሲፈልግ ምክርህን ለግሰው፣ ካስነጠሰውና ለአላህ ምስጋና ካደረሰ በጎ ምኞትህን ግለፅለት፣ ሲታመም ጠይቀው፣ ሲሞት ተከተለው (አስክሬኑን ወደ መቃብር ሸኝ)' ማለታቸው ተመልክቷል፡፡
* ከዚህ ሐዲስ ብዙ ነገሮችን እንረዳለን፤ ሰላምታ ማቅረብና መመለስ ግዴታ መሆኑ፣ በሽተኛን ሲታመም መጠየቅ፣ ግብዣን ማክበር፣ አስከሬን መሸኘት፣ ላስነጠሰ ሰው በጎ መመኘት (ምስጋና ለአላህ ካቀረበ)፣ ምክር መለገስ ለሚፈልግ ሰው … የኢስላም ልዕልናና የሙስሊሞች አንድነትና ወንድማማችነት ለመጠበቅ የሰጠው የላቀ ትኩረት ማሳያ ነው፡፡
ቁርዓን ሐዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
Download Islamic App:Abu Hurraira
play.google.com/store/apps/de...