Рет қаралды 44,934
ያስጀመረን እግዚአብሔር ማስፈጸምንም ያውቅበታልና፤ እንግዲህ ትምህርታችንን እያሰፋን፣ የእግዚአብሔርን የጦር መሳርያ እየያዝን የወንጌል ተደራሺነታችንን እያሳደግን፣ እንኳን ለታላቁ ዐቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ።ጾም ምሕረትን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የምናገኝበት ጸጋና በረከትን የምናፍስበት ኃጥያታችን የሚደመሰስበት ለሀገራችን ሰላምና ፍቅር የሚወርድበት ያድርግልን።
መልካም የሁዳዴ ጾም ይሁንላችሁ። ብዙ ሕዝበ ክርስቲያኖችን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር በረት እያመጣን ጌታ ያስተማረንን እውነትና ጸጋ በዓለም ፊት መግለጣችንን እንቀጥላለን፡፡
የቤተ-ሳይዳ የመጻሕፍትና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ መደብር አድራሻ ፦ 22 ማዞሪያ ጌታሁን በሻህ ሕንፃ ፊት ለፊት ከአክሱም ሆቴል ወረድ ብሎ ሀኮማል ባስራው አዲሱ ትጋት የገበያ ማእከል (አዲስ ቀይ ህንጻ) የመጀመሪያው ፍሎር ከንብ ባንክ ጎን ያገኙናል። ለበለጠ መረጃ ለዚሁ አገልግሎት ብቻ የሚውል በእነዚህ ስልክ መደወል ይቻላል 0919959995 P.O.Box 25084 Code 1000 ይህ ስልክ ሌላ አገልግሎት አያስተናግድም
በአምልኮተ እግዚአብሔር ኃይል በኩል ክፉ መንፈሶችን መዋጋት በጀመሩ እና የአጥፊ ጠላቶች ሴራና አሠራር ባልገባቸው ሰዎች መካከል የሚኖር መቋሰል አለ፡፡
በተለይ ደግሞ ውጊያውን ያልተረዱት ቤተሰቦች፣ የትዳር አጋሮች፣ ልጆች፣ ዘመዶችና የቅርብ ወዳጆች ሲሆኑ፤ በተግባራዊ የክርስትና መንገድ ላይ እየተጓዘ ባለው ሰው ላይ ብዙ የሕሊና እና የሞራል ቁስለት ይደርሳል፡፡
የዚህ ያለመግባባት ጠባይና በመንፈሳዊ ነጥብ ላይ አንድነትን ያለማግኘት መንስኤ፤ ከውስጥ ተመሳስለው ባደፈጡት የክፉ መናፍስት 'ተለያይቶ ማለያየት' በሚባል የጥፋት አሠራር የሚፈጠር የእምነት ኃይልንና ሰማያዊ ጉዞን የማዳከሚያ ጥበብ ነው፡፡
መንፈሳዊ ውጊያን የሚያውቅ ግለሰብ ውስጥ ያለው መንፈስ እና ምንም ስለ ውጊያ የማያውቅ ግለሰብ ውስጥ ያለው መንፈሰ መካከል ልዩነት አለ፡፡ መናፍስቱ ይሄን የውስጥ ልዩነት በመጠቀም፤ ሰዎቹ ከውጪም እንዲለያዩ መንገድ ይቀይሳሉ፡፡ ተለያይቶ ማለያየት ተብሎ የተገለጸው ጉዳይ ይሄ ነው፡፡ እናም መንፈሳዊ ውጊያን በመረዳት በክፉ መንፈሶች ላይ መረጃና ግንዛቤ ያገኙት፤ ያላገኙትን ሰዎች ለማንቃት የሚያደርጉት ጉዞ አብዛኛው የመደምደሚያው መድረሻ የተስፋ ቁስል፣ የእምነት ቁስል፣ የሞራል ቁስል የሚሆነውም በዚህ የመንፈሶቹ ከውስጥ የተለያዩበትን ሁኔታ ወደ ውጪ ወደ ሰዎች ሕይወት ግልጸው የማለያየት ሥራን ስለሚሠሩ ነው፡፡
በሃይማኖት ጦር ዕቃ በኩል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ጥቃት እየተሰነዘረበት ያለው የመንፈስ ሠራዊት፤ ሌሎች ያልነቁ ግለሰቦች ውስጥ ያሉት ወዳጆቹ እንዳይነኩበት በተቻለው አቅም ነገዱን የመጠበቅ ከለላን ያከናውናል፡፡ በዚህ ስለዚህ፤ አምልኮት የሚያውቀው ሰው የማያውቀው ሰው ጋር ገና ሲገናኝ፤ መንፈሶቹ ፈጥነው በመጠራራት ቀድመው ከውስጥ ተሰብስበው ይመካከራሉ፡፡
ይሄን ልብ ያላለው መንፈሳዊ ትግልን የተያያዘው ግለሰብም፤ ሌላውን የረዳ መስሎት እንደወረደ ስለ ክፉ መንፈሶች አሠራር፣ ስለ መስገድና መጸለይ ጠቀሜታ፣ ስለ በረከትና የሰላም ኑሮ የተረዳውን ያህል መናገር ሲጀምር፤ ቀድመው ከውስጥ ተመካክረው የማለያየት ዓለማ ይዘው የተሰለፉት መንፈሶች የተናጋሪው ድምፅ ላይ ተቀምጠው፤ የአዳማጩ ጆሮ ላይ ሆነው፤ ሁለቱም ሰዎች በሌላ ባዕድ ቋንቋ እየተነጋገሩ እስኪመስላቸው ድረስ በአሳብ መዘበራረቅ ውስጥ ገብተው በፍጹም ወደ አንድ የስምምነት ምዕራፍ እንዳይመጡ ያደርጋሉ፡፡ "ስለዚህም ስምዋ ባቢሎን ተባለ፥ እግዚአብሔር በዚያ የምድርን ቋንቋ ሁሉ ደባልቋልና፤ ከዚያም እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ እነርሱን በትኖአቸዋል። " (ኦሪት ዘፍጥረት 11፥9)