Рет қаралды 18,056
1 የሸሸና የኮበለለ አገልጋይ
2 ቁልቁል የወረደ አገልጋይ
3 እንደገና ወርዶ የተኛ አገልጋይ
#ሁላችንም_ልንማርበት_የሚገባ_ወቅታዊ_ልዩ_ትምህርት_Subscribe_Share_like_በማድረግ_አገልግሎቱን_ይደግፉ።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ሳክራሚንቶ ደብረሰላም ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን በየካቲት 17 / 2016 ዓ.ም February 25 / 2024 የተከናወነ የወንጌል እና የፈውስ አገልግሎት
እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ እኔ ደግሞ ሳውቀው በፍቅሩ በኩል ነው፡፡ ስለእርሱ ከፍቅሩ ውጪ ሌላ እውቀት እንዲኖረኝ አልሻም፡፡ እንዳፈቀርሁት በተሰማኝ ቁጥር ገና ምኑንም እንዳልጀምርኩት ገብቶኝ እገኛለሁ፡፡ ላላፈቅረው ስሞክርም፤ ድክመቶቼን ሁሉ ያውቃቸዋልና መልሶ በክንዱ ውስጥ ያኖረኛል፤ ሳይጫነኝ ይከብደኛል፤ ሳይናገር ያወራኛል፤ ራቅሁት ብዬ አቅጣጫ ስቀይር ከፊት ቀድሞ ወደራሱ ይመራኛል፡፡ አንዳንድ አባቶች "ኃይለኛው!" እያሉ ሲጠሩት እሰማለሁ፡፡ እውነትም እርሱ ኃያል ነው፡፡
ባሕሪይው ንጹሕና ቅዱስ ነው፡፡ በእርሱነቱ ቤት ውስጥ እውነት ብቻ አለ፡፡ ከሁሉ የሚገርመኝ ግን ገርነቱ ነው፡፡ እያየ ዝም፣ እየሰማ ዝም፣ እያወቀ ዝም፡፡ ይህን በጥሞና ባሰብሁ ጊዜያት ላይ ነፍሴን እስኪቀዘቅዘኝ ድረስ መልካምነቱ ያንሰፈስፈኛል፡፡ ያደረኩበትን ሁሉ አስታውስና የምቆምበትን የመሬት ቦታ ሳይቀር እጠላለሁ፡፡ "እንደምን ያለው ዓመፀኛ ልጅ አለህ?" እለዋለሁ፡፡ እርሱ ግን እቅፉን ከዙሪያዬ በቀንም በሌትም አያነሣም፤ ይወደኛል!
ምን ባደርግለት በቃ እል ይሁን? ምን ብሆንለት ደስ ይለው ይሁን? ምን ብሠራለት እረካ ይሁን? .. በብዙዎች ዘንድ ስለ ሃይማኖት ሲነሣ የመድረሻውን ነጥብ ከገነት አሊያ ከሲዖል አንጻር ያስቡታል፡፡ ትክክል የሆኑበት የራሳቸው እይታ አለ፡፡ ለእኔ ግን ይህ አያሰጨንቀኝም፡፡ ይሄን ዓለም ተሻግሬ ስለምደርስበት ቦታ ማሰብ አያሳስበኝም፡፡ ይልቅ እስከፈቀደልኝ የምድር ቀኔ ስሙን ማውሳት እፈልጋለሁ፤ በዮርዳኖስ አንቀጽ "የምወደው ልጄ" የሚል ድምፁን ማድመጥ እመርጣለሁ፤ እመቤቲቱን ካየሁበት ከመስቀሉ ግርጌ መቆምን እፈቅዳለሁ፤ እንደ ጴጥሮስ "ትወደኛለህን?" እያለ ሦስቴ እንዲጠይቀኝ አልማለሁ፡፡
ሙሴ ከፍርድ ሸሸ ግን እግዚአብሔር ተጠቀመበት ዮናስ ከእግዚእብሔር ፊት ሸሸ እግዚአብሔር ግን ተጠቀመበት ። ሳምሶን የማትገባ ሴት ዘንድ ገባ
ያዕቆብ በክቡ ውስጥ ሮጠ ፤ ሳራ ተስፋ ቆረጠች ፤ ሎጥ ከተሳሳተ ህዝብ ጋር አብሮ ተጓዘ አምላክ ግን ሁሉንም ተጠቅሞባቸዋል።