Рет қаралды 36,916
በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ፥ መዝሙረ ዳዊት 45 :16
ገና በእግዚአብሔር ቤት እናገለግላለን
ገና የጠፉትን በጎች እንፈልጋለን
ገና በዲያቢሎስ አሰራርና ስልት ውስጥ
ያሉ ሰዎች በእግዚአብሔር ኃይል ይፈወሳሉ
ገና ዓለምን እንዞራለን ወንጌል በዓለም ይሰበካል
ገና የተቸገሩትን ሰዎች እንረዳለን
ገና ቤተክርስቲያን እናንጻለን።
ገና በሌሎች ስቃይና መከራ ውስጥ ምርኩዝና
ድጋፍ እንሆናለን ፣
ገና የወደቁትን እናነሳለን ፣
ገና የተናቁትን እናገለግላለን ፣
ገና ድቤ የሚመቱን፣ ባለሦስት ጡት ጀበና የሚይዙትን፣ የተብረቀረቀ ልብስ የሚለብሱትን፣ ለጠቋርና አዳል ሞቲ የሚሰግዱትን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር እንመልሳለን ማንን ይዘን? አንድ አምላክን ይዘን!
ሳይገባን መተት በሽታ ሆኖ አስሮናል፡፡ ፡፡ ሳይገባን ዓይነጥላ ገንዘባችንን ገንዘቡ አድርጎታል፡፡ ሳይገባን ዛር ትዳራችንን አደጋ ላይ ጥሎታል፡፡ ሳይገባን ፍቅር አጥተናል፡፡ ሳይገባን ገንዘብ ቸግሮናል፡፡ ሳይገባን ዕውቀት አጥፍቶናል፡፡ ሳይገባን አጋንንት ቀድሞናል፡፡ ሳይገባን መኖር አላወቅንበትም፡፡ ሳይገባን ሌሎችን ጎድተናል፡፡ ሰድበናል፣ አሸማቀናል፣ አዋርደናል፣ ደብድበናል፣ አሰቃይተናል፣ አሰድደናል፣ አስርበናል፣ አስጠምተናል፣ ፍቅር ከልክለናል፣ ምሕረትን አጨናግፈናል፣ በጨለማ ጭነን ሰደናል፣ አፈናቅለናል፣ ሕጻናትን አርደናል፣ ሴቶችን እናቶችን አስለቅሰናል፡፡ እስኪ ተናገሩ በምድሪቱ ሳይገባን ምን ያላደረግነው አለ? ሕይወታችንን ቆም ብለን ማየት ተስኖን፤ ሳይገባን እያልን በውጤቱ እየማሰንን፤ መንስኤውን አጣነው፡፡ ሳይገባኝ ከዲያቢሎስ ክስ አያስጥልም፡፡ ቀድሞውኑ እንዳይገባህ ነው የሚታገልህ፡፡ ሳይገባኝ ካልክ ውስጥህ የተደበቀው አጋንንት ከ'7 ዓመታት በኋላ ዓይንህ ላይ ይቀመጥና ታስተላልፈዋለህ፡፡ ቡዳ ትሆናለህ፡፡ የገዛ ልጅህን ትበላዋለህ፡፡ የገዛ ወዳጆችህን ትለክፋቸዋለህ፡፡
እኔ ምቀኛ አይደለሁም፣ ጠንቋይ ጋር አልሄድም፣ ስለ መተት አላውቅም አንተን አያስጥልህም፡፡ ምቀኛ ካልሆንክ የሚመቀኝብህ አለ፡፡ ጠንቋይ ጋር በህልምህም ሄደህ ባታውቅ፤ የቄስ ዘር ቢኖርክ ጠንቋይ ጋር የሄደው ሰላምህን ይፈልገውና ይረብሽሃል፡፡ መተትን ባታውቅ መተተኛ ያውቅሃል፡፡ ሰይጣን ላይ አልደርስ የት አውቄው አይሰራም፡፡ ሳታየውና ሳትሰማው የሚገባ ጠላት ልብህ ውስጥ ልብ ከመሆን ያንተ አለማውቅ ምን ያግደዋል?
አትሞኙ፡፡ እናንተ ያገኛችሁትን ዕድል ብዙዎች ተመኝተው አጥተውታል፡፡ እናንተ ያላችሁን ጊዜ ብዙዎች ደም እንባ አልቅሰው አላገኙትም፡፡ እናንተ የሚሰጣችሁ መረጃ ለሌላ ለሚገባው ቢደርስ ምን እንደሚያደርገው የቸገረው ብቻ ያውቀዋል፡፡