Рет қаралды 31,266
ዛሬ ሰኔ 3 / 2015 ዓ.ም በሰሚት ዋሻ መካነ ሕይወት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በተካሄደው ጉባኤ ከአሶሳ ድረስ ይህንን መንፈሳዊ ጥሪ በFacebook አይታ በመምጣት ድንገት የተጋለጠው እርኩስ መንፈስ እና የእግዚአብሔር ማዳን
እግዚአብሔር ለአባቶቻችን በዘመናቸው ሲያሳየቸው የነበረውን የፍቅሩን ስጦታ እኛ ለማየት አልታደልንም፡፡ ምክንያቱም ተለይተን አልወጣንም፡፡ ከልምዳችን አልተለየንም፡፡ በዓለም ውስጥ ከሰበሰብነው እውቀት አልተለየንም፡፡ ብዙ ገንዘብ ለማምጣት ከምንደክምበት ቦታ አልተለየንም፡፡ በመሆኑም ከአባታችን ቤት በስተኋላ ባለ የቤተሰብ ሰንሰለት ውስጥ ራሱን አስገብቶ በስውር ተዳብሎን የቆየው አጥፊው መንፈስ፤ እግዚአብሔር ያዘጋጀልንን እንዳናይ ከሰማያዊ እውነት፣ ከመለኮታዊ ምሪትና ከእምነት ኑሮ ለይቶ ወደ ዓለም አወጣን፡፡
አንድ ጊዜ ቆም እንበልና እስኪ ትውልዳችንን እንመልከተው፡፡ እንዴት እየኖርን ነው? ምን እያስተናገድን እንገኛለን? ምን እያየንና እየሰማን ነው? የዕለት ዜናዎቻችን ምን ይናገራሉ? ኸረ የሰማይ አባታችን ቃል የሚለው እንዲህ ነው፡፡ "ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።"
#like_Comment#Share__በማድረግ_አገልግሎቱን_ይደግፉ።