Рет қаралды 36,310
Subscribe, Share, Like, Comment እያደረጋችሁ ላልሰሙት አሰሙ ላልነቁ አንቁ! መንፈሳዊነት ይብለጥ! የማዳመጥ ጊዜ ላይ ነን!!!
እጅግ በቁጥር የበዙ ሰዎች ስሜታቸው ከመለዋወጡ በፊት፤ ስሜታቸው እንዲለወጥ ከውስጥ የሚገፋ ኃይል እንዳለባቸው ልብ አይሉትም፡፡ ምክንያቱም፤ መናፍስቱ ከውስጥ ሆነው በኛ አሳብ ልክ ሲጣሉን፤ ራሳችንን በራሳችን የምናወራ እንጂ ከሌላ ባዕድ ፍጡር ጋር እየተዋጋን እንደሆነ አናስተውልም፡፡
ርኩስ መናፍስት የጥፋት አሳባቸውን ወደ ጥፋት ግብር ከመቀየራቸው በፊት ሁልጊዜ መቼት የሚባለውን "መቼ" እና "የት" የሚለውን የሥነ ጥበብ ሕግ ይጠቀሙታል፡፡ ይኸውም፤ መቼ የጥፋት አሳብ ማመንጨት፣ መቼ የጥፋት ግፊት መጨመር፣ መቼ የጥፋት ግብርን ማጽደቅ የሚል፤ ጊዜን ከውስጥ ወደ ውጪና ከውጪ ወደ ውስጥ የመጠበቅ ሂደት ይጓዙበታል፡፡ የት ብለው በሚጠብቁት የቦታ መምረጥ አሠራር ውስጥ፤ የት ሥፍራ ላይ ጥፋቱን እንደሚመሩ፣ የውስጥ ጫናውን እንደሚፈጥሩ፣ የግብር ሂደቱን እንደሚያስፈጽሙ እኛ ውስጥ ሆነው ያቅዳሉ፡፡ ምሳሌ ስንመለከት፤ በመንፈሳዊ ጥንካሬና መረዳት ውስጥ ባለንበት ሰዓትና ቦታ ላይ መናፍስት ዝም ይላሉ፡፡ ከጊዜያት ቆይታ በኋላም ወደ ሥጋዊ አኗኗርና ድክመት የምናዘነብልበት ጊዜና ቦታ ሲመጣ፤ ከውስጥ ሆነው የመጣላት እቅዳቸውን ከውጪ በመጣው አጋጣሚ አስታከው ለመፈጸም ይታገላሉ፡፡