Рет қаралды 39,573
ዳሩ ግን ፅድቁን እና መንግሥቱን ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። የሉቃስ ወንጌል 12:
31
አብዛኛው ሕብረተሰብ የእግዚአብሔርን የማዳን ነገር ዋጋ ሳይሰጡና በበጎነት ሳይመለከቱ፤ የራሳቸውን ምክንያት በመደርደር፤ ሰው ላይ የሚታየውን ችግር ፋይዳ ቢስ አድርገው፤ ባዶነታቸውን ሳይመለከቱ እንደ ነፍሳቸው ምኞት ይናገራሉ፡፡ “እንዲሁም ክፋትን ይጎነጉናሉ” ብዙው ሰው ረጅሙን ዕድሜ ያሳለፈው በምስጋና፣ በፀሎትና በአምልኮት ሳይሆን፤ በጥላቻ፣ በመለያየት፣ በመሰሪነትና አንዱን አንዱ ጥሎ በማለፍ ስለሆነ፤ በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ሆኖ ኃጢአያትን በመለማመድ፤ ደፋር፣ ኩሩ፣ ቀማኛና ነጣቂ በመሆን፤ ክፋትና ጥፋትን ለማቆየት እየሠራ ይገኛል፡፡
እኛም ታዲያ የምናስበው፣ የምናቅደውና አመለካከታችን ከክፋት ጋር የተያያዘ በመሆኑ፤ የብዙውን ትውልድ ዕድል አጥፍተን፤ ብዙ ከሃዲዎችን ማፍራታችን አንዱ የግፍ ሥራችን ምልክት ነው፡፡ በጎና ቅን ሆነን በመንፈስ ቅዱስ ተዋጅተን ወደ ሰው የምንሄድበት ሕሊና ስላጣን፤ ነገር እየጎነጎንን መሰሪ እቅድ ኑሯችን ውሰጥ ተክለን፤ ከጀርባችን ብዙ ክፋቶችን አዝለን እንኖራለን፡፡
ከእነሱ ሁሉ የተሻለው እንደ አሜኬላ ነው” ያለው የነብዩ ቃል፤ አሜኬላ ተደብቆ የሚወጋ ከታች ስትረግጠው ከላይ የሚቧጥጥ፣ ጫማ አልፎ የሚያቆስል፣ የሚያደማ፣ የማያስሮጥ፣ ቁስል የሚሆን፣ እግርን የሚቆጠቁጥ፣ የሚያም፣ የሚያስጨንቅ፣ አረማመድን የሚገታ፣ የወደፊት ተስፋን የሚያመክን እና ቁልቁል የሚያሽከረክር ነው፡፡ ዛሬም የተሻለ የተባለው ሰው ሁሉ ልክ እንደ እሾህ የሚዋጋ ሆኖ በሥልጣን፣ በማዕረግ፣ በከፍታ ለሌላው ሰው እንደ አሜኬላ ሆኗል፡፡ ስለዚህ ከሁሉ ቅን የሆነውም፤ እንደ ኩርንችት ነው፡፡ ኩርንችት ደግሞ እንደ ደበኛ አድፋጭ፣ ተንኮለኛ፣ ምቀኛና ነገረኛ ምሳሌ በመሆን፤ በተፈጥሮ ሂደትም በምትረግጥበት ስፍራ ላይ እግርህንና ኮቴህን ተደብቆ የሚወጋ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ኩርንችትና አሜኬላ በሁሉም አቅጣጫ በኑሮችን ውስጥ የተለመደ አድርገን፤ በክፋትና በግፍ አሠራር የሌሎችን ሕይወት በግልጽና በስውር ስንጎዳ ይታያል፡፡
ለተጨነቀች ነፍስ ሁሉ ትደርስ መፅናኛም ትምህርትም ትሆናት ዘንድ #Share. አድርጉት!
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
ከ መልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ ( የአባቱ ልጅ )
02/06/2014 ዓ.ም
ከሕይወት ተራራ ላይ መንፈሳዊነት ይብለጥ!
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯