Wow……..what a powerful message, real expository, taking the time enough to stay at every verse to read, observe, expose, and apply surrendering each individual to be searched by the Holy Spirit. What a fitting song and a prayer of repentance. Dear Lord come to us, restore us, help us live it out please 🙏 ዮሐንስ 6:68፤ ስምዖን ጴጥሮስ፦ “ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤ ዮሐንስ 6:69፤ እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ አምነናል አውቀናልም፡” ብሎ መለሰለት። መዝሙር 1:1፤ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። መዝሙር 1:2፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። መዝሙር 1:3፤ እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። መዝሙር 1:6፤ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና፥ የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።