Рет қаралды 5,940
ለተጨነቀች ነፍስ ሁሉ ትዳረስ መፅናኛም ትሆናት ዘንድ #share #share በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ በሰው ዘንድ ቢሟጠጥ ተስፋ እና ደስታ እኛስ ፈጣሪ አለን ሁሉን የሚረታ!
"ወርእዮ ብዙኃነ ሰብአ መሐሮሙ እስመ ስሩሓን እሙንቱ ወግዱፋን ከመ አባግዕ ዘአልቦ ኖላዌ። - ብዙ ሕዝብም ባየ ጊዜ፥ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች ተጨንቀው ተጥለውም ነበርና አዘነላቸው።" ማቴ. 9፥36
እረኛ አልባ በጎች ስምሪት የላቸውም፡፡ ስለዚህ የለመለመ መስክ አያገኙም፤ ወደ ዕረፍት ውኃም አይደርሱም፡፡ ይልቁን ይቅበዘበዛሉ፤ እርስ በእርስ ይገፋፋሉ፤ በየፊናቸው ይነጉዳሉ፤ ወደየፍላጎታቸው ይሄዳሉ፡፡ ምናልባት ጉዞአቸው ከተኩላዎች መንደር ይመራቸውም ይሆናል፡፡ እረኞችም በበኩላቸው የዋሽንት መክሊታቸውን በተመለከተ ብርቱ ክርክር ሊገጥሙ ይችላሉ፡፡ በመሆኑ መንጋዎቻቸው ይራባቸው፣ ይጥማቸው አያውቁ ይሆናል፡፡ ደ'ሞም እኮ እነርሱም ይርባቸዋል፡፡ በዚያ ላይ ጎተራው እህል ሊቀንስበት አይገባም፤ ሲሆን ሊበዛለት እንጂ፡፡ ስለሆነ አንዲቱ ግልገል ለሁለት ቀን ቁርስና ምሳ የምትበቃበትን ዘዴ ማወቁ ይበጃል፡፡ ስለዚህ..
እናጠቃልለው፡፡ ክርስትና እንደ ክርስቶስ መኖር ነውን ቢያንስ በመርህ ደረጃ አማኝ ሰዎች ይቀበላሉ፡፡ የማይቀበሉቱ፥ ፍቅርን ሰው እንደመሆን ይቀበላሉ፡፡ ፍቅርን የማይቀበል ካለም፥ ሁሉ ቢኖረው ፍቅር ግን ስለሌለው ምንም የሌለው፥ አየርን የሚከተል ከንቱ ሆኗል፡፡ (1ኛ ቆሮ. ምዕ 13) ለክርስቲያኖች ደግሞ፥ ፍቅር፥ በክርስቶስ አካልነት ያሉ ሕዋሳት መሆኛቸው ነው፡፡ አፍንጫን የምትገፋ ዓይን የለችም፡፡ ራስ የከበደው አንገት እስከአሁን የለም፡፡ እጅ የማይወደው እግር በእውኑ አለን?.. አለ የሚል ምእመን፥ እነሆ ለምእመናንና አገልጋዩ ሁሉ ፍቅር አይኖረው ዘንድ ተፈቅዶለታል፡፡ አገልጋዮም እንደዛው፡፡
እስቲ እንደወደደን እንዋደድ!
"አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ በፍቅሬ ኑሩ።" (ዮሐ. 15፥9)
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
ከ መልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
22/04/2015 ዓ.ም
ከሕይወት ተራራ ላይ መንፈሳዊነት ይብለጥ!
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯