Рет қаралды 120,544
#sileHiwet #ethiopia
እነዚህ ሁለት ሴቶች በዚህ ግቢ በየራሳቸው ቤት ከ20 ዓመት በላይ ሲኖሩ በመሀከላቸው ሊያግባባ የሚችል ቁርሾ በመፈጠሩ ዛሬ አንዳቸው ቤት ሀዘን ዘው ብሎ ገባ፡፡ ሆኖም የአሰገደች የአብራክ ክፋይዋ የሆነው በ17 አመቱ ቢኒያም ከወትሮ በተለየ ሁኔታ ከት/ቤት ሳይመለስ ሰአታት አለፈ ሆኖም የአንድ ልጇ ሳይመለስ በዛው የመቅረቱ ጉዳይ ውስጧን ያስጨነቃት አሰገደች ሰአታት ቢቆጠሩ ቁጥር የልብ ትርታዋ አብሮ እየመታ መቀመጥ አቅጧት መቁነጥነጥ ጀመረች፡፡ ምንም እንኳን ልጄ ይመጣል ብላ በር በሩን እያየች በጉጉት ብትጠብቅም ልጇ ግን አልመጣም፡፡ አሁን ይበልጥ ተረበሸች የወላድ አንጀት አላስቀምጥ ሲላት ፍለጋ ወጣች በደመ ነብስ የምትጓዘው አሰገደች ስለ ልጇ ብቻ እያሰበችና ስትሮጥ እንቅፋት ቢመታትም ህመሟን ዋጥ አድርጋ ልጇ ይኖራል ብላ ባሰበችበት ቦታ ሁሉ ፈለገችው፡፡ ነገር ግን ልታገኘው አልቻለችም፡፡ ከፍለጋ ተመልሳ ስልክ ደግማ ደጋግማ የተለያዩ ቦታዎች ብትደውልም ልጇ ቢኒያም አየው የሚላት አጣች በስተመጨረሻ ግን የፈራቸው ደርሶ እንደ አይን ብሌን የምታየው አንድ ልጇ ጉዳት ደርሶበት ሕይወቱ ማለፉን ቤቷ ተቆርቁሮ በሰማች ጊዜ ሰማይና ምድሩ ተደበላለቆባት ጩህቷን አምባረቀችው፡፡ አሰገደች አሁን በቤቷ የሀዘን ወላፈን ሲገርፋት በሌላ በኩል ደግሞ ጎረቤቷ በቀለች አሰገደች ሀዘን ውስጧ በደስታ ተሞልቷል፡፡ ታዲያ እኝህ ሁለት ሴቶች በፈጠሩት አለመግባባት ከ20 አመት በላይ ሲነታረኩ ኖረው ዛሬ የአሰገደች ልጅ ነፍስ በሰው እጅ ሲጠፋ ግን የአብራኬ ክፋይ የቢኒያም ነብስ እንዲጠፋ ያደረገችው ጎረቤቴ በቀለች ናት ብላ አሰገደች ለፖሊስ አቤቱታ ያቀረበችው ሳትውል ዛታድር ነው፡፡ ሆኖም የልጇ ሞት ያንገበገባት አሰገደች እርግጠኛ ሆና አንዱ ልጄን አስገድላብኛለች ብላ ለመርማሪ ፖሊስ በጎረቤቷ በቀለች ላይ ጥቆማዋን ስትሰጥ በሙሉ እምነት ነበር፡፡ ሆኖም ጠቆማ የደረሰው መርማሪ ፖሊስም በወጣቱ ሞት ምክንያት ብዙ ስራ እንደሚጠብቀው እያመነ የዚህ ውስብስብ የወንጀል ታሪክ ለመፍታት ስለነበረው ቁርሾ ከአሰገደች ዝርዝር እውነታውን ሲዳሰስ የቀድሞ የበቀለች ባል ተስፋዬ ከ 20 አመት በፊት በተፈጠረ አለመግባባት ትዳራቸው የፈረሰ ሲሆን እንደበቀለች እምነት ግን ትዳሯ እንዲፈርስ ምክንያቷ አሰገደች ናት ብላ ነው የምታስበው፡፡ ታዲያ ይህ በቀል እንደተቋጠረ ውሎ አድሮ በቀለች አሰገደችን 20 አመታትን ጠብቃ የበቀል ፈላፃዋን መለሰችለት የሚለውንና ሌሎች በታሪኩ የሚደሰሱ አጓጊ ክንውኖችን ይከታተሉ እያልን ጋበዝናችሁ፡፡